ከ140 በላይ በስልጣን ላይ ያሉና የነበሩ የአለም ሀገራት መሪዎች ፣ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ከክፍያ ነጻ እንዲሆን ጠየቁ ።

ሀገራቸውን እየመሩ ያሉና ቀደም ሲል ሀገራቸውን በጠቅላይ ሚስትርነትና በፕሬዝዳንተነት ያገለገሉ ፣ ከ140 በላይ መሪዎች ፣ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ከክፍያ ነጻ እንዲሆን መጠየቃቸው ተነግሯል ።

ክትባቱ የፈጠራ የባለቤትነት መብት እንዳይጠየቅበት እና ህክምናውም ነጻ እንዲሆን መሪዎቹ ጠይቀዋል ተብሏል ።

አልጄዚራ እንደዘገበው ፣ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ከክፍያ ነጻ እንዲሆን ከጠየቁ የሀገር መሪዎች መካከል የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚደንት ሲሪያል ራማፎዛ እና የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካሀን እንደሚገኙበት ተገልጿል ።

ቀደም ሲል ሀገራቸውን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እና በፕሬዚደንትነት ያገለገሉት እንደ ጆሴ ማኑኤል ባሮሶ፣ ጎርደን ብራውን እና ኤለን ጆሴፍ ሰርሊፍ ክትባቱ ከክፍያ ነጻ እንዲሆን ከጠየቁት የቀድሞ ሀገር መሪዎች መካከል ናቸው ተብሏል ።

የአለም ጤና ድርጅት አካል የሆነው የአለም ጤና ጉባኤ ( WHA ) በሚቀጥለው ሳንምት አመታዊ ጉባኤ ያካሄድል ፣ የሀገሪቱ መሪዎች ጥያቄም በዚሁ በጉባኤ ይቀርባል መልስም ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

የመሪዎችን ፊርማ የያዘው እና ለ WHA የቀረበው ደብዳቤ ተቀባይነት እንዲያገኝ የሁሉም አለም ሀገራት መንግስታት እና አለም አቀፍ ተቋማት በጋር መቆም አለባቸው ብለዋል መሪዎቹ ።

ደህንነቱ የተጠበቀ እና ውጤታማ የሆነ ክትባት ሲገኝ በሁሉም የአለም ሀገራት በፍጥነት እንዲሰርጭም ጠይቀዋል።

በተመሳሳይ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከልከል እና ለመቆጣጠር የሚያገለግል ማንኛውም ቴክኖሎጂ ከክፋያ ነጻ እንዲሆን ተጠይቋል ።

የአሜሪካን መንግስት ክትባቱን ለማግኘት በሚደረገው የምርምር ሂደት የገንዘብ ድጋፍ እያደረገች በመሆኑ ክትባቱን ቅድሚያ እንድታገኝ ይደረጋል ተብሏል ።

የፈረንሳይ መንግስት በበኩል ክተባቱ ለአሜሪካ ቅድሚያ ይሰጣል መባሉ ተገቢ አይደለም በማለት ማጣጣሉ ተነግሯል።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በዳንኤል መላኩ
ግንቦት 7 ቀን 2012 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.