በኢትዮጵያ ተጨማሪ 190 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ የ 5 ሰዎች ህይወት ደግሞ ማለፉ ተገልጿል።
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4,995 የላብራቶሪ ምርመራ 190ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2,336 መድረሱን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።
በዛሬው ዕለት በኮሮና ቫይረስ 5 ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ያፉ ዜጎች ቁጥር ወደ 32 ከፍ ብሏል።
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8
ኢትዮ ኤፍ ኤም የኢትዮጵያዊያን
ሰኔ 2 ቀን 2012 ዓ.ም











