የአዉሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የአንበጣ መንጋን ለመከላከል 9 ሚሊዮን ዩሮ ሰጠ፡፡

ድጋፋ በሃገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተዉን የበርሃ አንበጣ መንጋ ለመከላከል ለምታደርገዉ ጥረት የሚዉል ነዉ ተብሏል፡፡

ይህን ያሉት የህብረቱ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦሬልና የህብረቱ የአደጋዎች መከላከል ኮሚሽነር ጃኔዝ ሌናሬክ በሶማሊያ ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በጋራ በሰጡት መግለጫ ላይ ነዉ፡፡

ሌናሬክ አክለዉም የተደረገዉ ድጋፍ ህብረቱ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር ያለዉን ጠንካራ አጋርነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ በቀጣይም በጎርፍ፣በድርቅና በተለያዩ አደጋዎች የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ድጋፋን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታዉቋል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8
በሙሉቀን አሰፋ
ጥቅምት 3 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.