ሳውዲ አረቢያ በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት መቀመጫ ስታጣ ቻይና እና ሩሲያ ብዙም ተቃውሞ አልገጠማቸውም ተብሏል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ባካሄደው ሚስጥራዊ ድምጽ 15 አገራት 47 አባላት ላሉት ምክር ቤት መመረጣቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በእስያ-ፓስፊክ ምድብ ውስጥ አራት መቀመጫዎች ብቻ የተገኙ ሲሆን ሳውዲ አረቢያ በቻይና ፣ በፓኪስታን ፣ በኔፓል እና በኡዝቤኪስታን ተሸንፋለች፡፡
ሩሲያ እና ኩባ እንዲሁ ያለምንም ተፎካካሪ ከምድባቸው በምክር ቤቱ መቀመጫ ማግኘታቸውን አሶሺዬትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
በደረሰ አማረ
ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም











