ባለፉት ሶስት ወራት ከ412 ሚሊዮን በላይ ብር ተመዝብሮ የነበረ ገንዘብ ማስመለሱን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ሕግ አስታወቀ።

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በተያዘው በጀት ዓመት ውስጥ ባለፉት ሶስት ወራት በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ላይ ናቸው።

አቃቢ ህጉ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የህግ ማስከበር እና የወንጀሎችን ህግ ማስከበር በ3 ወራት ውስጥ 12 ሺህ 37 ክሶች ላይ አቃቢ ህግ ውሳኔ ሰጥቷል።

የኢኮኖሚ ወንጀሎችን በተመለከተ በተለያዩ ምክንያቶች ተመዝብረው ከነበሩ የህዝብ ሀብቶች ከ412 ሚሊየን በላይ የሚገመት ብር ማስመለስ ተችሏል ብለዋል።

የህግ ማዐቀፍን በተመለከተም የንግድ ህግ ፣ የወንጀል ህግ ስርዓት እና የማስረጃ ህግ እና የግልግል ዳኝነት ህግ ዝግጅትን በተመለከተ ጠንካራ ስራ መስራቱን ጠቅላይ አቃቡ ህጉ ተናግረዋል።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በዳንኤል መላኩ
ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.