የአለም ባንክ ለኮሮና ቫይረስ ክትባት የሚዉል 12 ቢሊዮን አሜሪካን ዶላር በጀት አጸደቀ፡፡

የአለም ባንክ በዛሬው እለት በማደግ ላይ ላሉ አንድ ቢሊዮን ለሚሆኑኑ የተለያዩ ሀገታት ዜጎች፤ በተለይ ለኮሮናቫይረስ ክትባት የሚውል 12 በሊዮን ዶላር በጀት መድቧል፡፡ ባንኩ እስካሁን ድረስ ለ111 ሀገራት ገንዘቡ ደርሷል ሲል አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

የአለም ባንክ ፕሩዘዳንት የሆኑት ዴቪድ ማለፓስ እንደተናገት አሁን በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት ፍተሃዊ የሆነ የኮሮና ቫይረስ የክተትባት ስርጭት እና አቅርቦት እንዲኖረቸው እየሰራን ነው ብለዋል፡፡

ፕሬዘዳንቱ አያይዘውም በተለይም በኢኮኖሚ በማደግ ለይ ያሉ ሀገራት ትልቅ ትኩረት እንደሚሻቸው በመግለፅ፤ ድህንነቱ የተጠበቀና ወጤታማ የሆነ ክትባት እንዲመረት በሎም ወቅቱን የጠበቀ ስርዐጭትም በእጅጉ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

አለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ዋና የአለም ባንክ አበዳሪ የግል ተቋም ሲሆን፤ በ 4 ቢሊዮን ብር በጀት የኮሮና ቫይረስ በሽታ መከላከያ፤ መቆጣጠሪያ እና ክትባትን ለማምረት ኢንቨስት እያደረገ ይገኛል፡፡

ተቋሙ እንገለጸው በዚህ ሰአት በአለም ዙሪያ ለ 1 ሚሊዮን ሰዎች ሞት፤ ከ 38 ሚሊዮን በላይ ለሞሆኑ በበሽታ ለለከፈው እና ሚሊዮኖችን ስራ አልባ በማድረግ ለድህነተ ለዳረጋቸው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ፤
ክትባት ማምረት እጅግ ወሳኝ ነው ብሏል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በጅብሪል ሙሀመድ
ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.