ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ ምርጫውን እንዳያሸንፉ እየጸለዩ መሆኑን የፍልስጤም ጠቅላይ ሚንስትር ተናገሩ።

የፍልስጤማዊን ጠቅላይ ሚኒትር ሙሀመድ ሺታያህ ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የህዳሩን ምርጫ የሚያሸንፉ ከሆነ መጪው ጊዜ ለአሜሪካም ሆነ ለአለም ከባድ ነው የሚሆነው ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ከአውሮፖ ህብረት ህግ አውጪዎች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ነው ይህንን አስተያየት የሰጡት፡፡

ባለፉት አራት አመታት የትራምፕ አስተዳደር ፍልስጤማዊንን በእጅጉ ጎድቷል ብለዋል በንግግራቸው፡፡

ከፕሬዝደንት ትራምፕ ጋር ሌላ አራት አመት የምንኖር ከሆነ ፈጣሪ ይርዳን …..ፈጣሪ ይርዳችሁ…..እና ፈጣሪ መላው አለምን ይርዳ ብለዋል፡፡

ይህንን አስተያያታቸውንም በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ለጥፈዋል፡፡

ነገሮች በአሜሪካ ውስጥ የሚለወጥ ከሆነ ይህ በእስራኤልና በፍልስጤም ላይም ይሆናል ማለታቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

የህዳሩን ምርጫ የዲሞክራቱ እጩ ተወዳዳሪ ጆ ባይደን ቢያሸንፉ እንደሚመርጡ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እርሱ በሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ጥሩ መረዳት አለው ያኔ የፍልስጤም-አሜሪካ ግንኙነት ይሻሻላል ብለን እናምናለን ሲሉም አክለዋል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በያይኔአበና ሻምበል
ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.