ባለፉት 24 ሰአታት ውስጥ በስፔን 16 ሺህ 973 የተጠቁ ሲሆን 156 ያህሉ ደግሞ ህይወታቸው አልፏል፡፡
እንደ አውሮፓውያኑ ከየካቲት 2020 በስፔን ቫይረሱ ከገባ አንስቶ እስካሁን ተጠቂው 1 ሚሊዮን 5 ሺህ 295 መድረሱን ቢቢሲ ዘግቧል።
ከአውሮፓ አንድ ሚሊዮን በማለፍ የመጀመርያ ብትሆንም ከአለማችን ሀገራት አሜሪካን፣ ህንድን፣ ብራዚልን፣ ሩሲያንና አርጀንቲናን በመከተል ስድስተኛ ነች፡፡
በሔኖክ አስራት
ጥቅምት 12 ቀን 2013 ዓ.ም