ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ኤርባስ ኤ 350 እቃ ጫኝ አውሮፕላን ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት ሞምባይ ከተማ አረፈ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ 350 ባጋጠመው የሃይድሮሊክ ችግር ምክንያት በህንዷ ሞምባይ ከተማ ለማረፍ መገደዱን ከአቪሽን ጋር የተገናኘ ዜናዎችን የሚያወጣው ሲንፕል ፍላይንግ ዘግቧል፡፡

አውሮፕላኑ ከሪያድ ወደ ህንዷ ባንጋሎር ከተማ እቃ ጭኖ በመጓዝ ላይ ሳለ የሃይድሮሊክ ፍሳሽ ስላጋጠመው መሆኑ ዘገባው ጠቁሟል።

አውሮፕላኑ አቅጣጫውን የቀየረው ለሁለት ሰአት ተኩል ያህል ከበረረ በኃላ መሆኑም ተነግሯል፡፡

አውሮፕላኑ 8 ሰራተኞችን የጫነ ሲሆን የጭነት አገልግሉት የሚሰጥ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በአሁን ጊዜ ይህ እክል የገጠመው አውሮፕላን በዚችው ሞምባይ አየር ማረፊያ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በያይኔአበባ ሻምበል
ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.