ፑቲን ሶሪያዊያን ስደተኞች ወደ ሀገራቸውን እንዲመለሱ እና ሶሪያንም መልሰው እንዲገነቡ ጥሪ አቀረቡ።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲ አብዛኛው የሶሪያ ግዛት በአሁኑ ወቅት አንጻራዊ ሰላም በመኖሩ በሚሊየን የሚቆጠሩት ሶሪያዊያን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው በመመለስ ሶሪያን መልሶው መገንባት አለባችሁ ብለዋል ።

የሶሪያን ጉዳይ በቅርበት የሚከታተሉ ታዛቢዎች ግን በሀገሩቱ ያለው ፣ በተላይም በምዕራብ በኩል ያለው ጦርነት ብዙሃን ስደተኞችን ለመመለስ አሁን ጊዜው አይደለም ብለዋል ።

ሩሲያ ለሶሪያው ፕሬዝዳንት በሽር አላሳድ በምታደርገውን የጦር ድጋፍ ለሀገሪቱ የእርስ በእርስ ጦርነት እና ለንጹሐን ግድያ ትልቅ ድርሻ ያላት በመሆኗ በተደጋጋሚ ትችት እንደሚቀርብባትም ተነግሯል ።

ከበሽር አላሳድ ጋር በ video call በአካሄዱት ውይይት ፑቲን ደማስኮ ዜጎቿን ለመቀበል ከነገ ጀምሮ እቅድ ትያዝ ብለዋል ።

አልጄዚራ እንደዘገበው ፣ ሞስኮ የሶሪያ ስደተኞችን ያለፍላጎትታቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ መወሰኗን ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ከአሜሪካ ባለስልጣናት ወቀሳ ተሰንዝሮባታል ።

አለም አቀፍ ሽብርተኝነት በእጅጉ መቀነስ ስለተቻለ ዜጎች ወደ ሀገራቸው በመመለስ እና በሂደት መደበኛ ኑሮ መጀመር እንዳለባቸው ፑቲን ተናግረዋል ።

በሶሪያ በ 9 አመታት ውስጥ በተካሄደ የእርስ በእርስ ጦርነት 500 ሺህ ዜጎች ተገድለዋል ፣ 5 ነጥብ 6 ዜጎች ሚሊየን ዜጎች ደግሞ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዋል እንዲሁም በጦርነቱ 6 ሚሊየን ዜጎችን የሀገር ውስጥ ስደተኛ አድርጓቸዋል ተብሏል ።

በዳንኤል መላኩ
ሕዳር 1 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.