በንግድ ማጨበርበር ሊታጣ የነበረ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ቀረጥና ታክስ ሊሰበሰብ መሆኑንም የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው በአዳማ እና ሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በድምሩ ከውጭ የገቡ የምግብ ዘይትና ጫማ መከፈል የነበረበት እና በተሳሳተ ዕቃ መግለጫ መንግስት ሊያጣው የነበረ 16 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ቀረጥና ታክስ ተደርሶበት እንዲሰበሰብ መወሰኑን ገልጧል፡፡
በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር እንዲገባ የተፈቀዱ የምግብ ፍጆታዎች ቢኖሩም ፤ በአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ከተፈቀደላቸው ታሪፍ ቁጥር ውጪ 14 ሚሊዮን ብር 508 ሺህ 328 ብር ከ 28 ሳንቲም ፤ ቀረጥና ታክስ አጭበርብረው ሊያስገቡ ሲሞክሩ ተደርሶባቸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በሞጆ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት በዲክላራሲዮን ቁጥር 4-27474/20 የተመዘገበ ዕቃ አስመጭው ቀረጥና ታክስ ከፍሎ በገቢ ዕቃ አወጣጥ በኩል በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ለእቃው መልቀቂያ ከተሰጠው በኃላ በኢንተለጀንስ በኩል በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ቀደም ሲል ከተገለፀው እቃ ልዩነት ተገኝቷል ብሏል ሚኒስቴሩ::
በዚህ የእቃው አገላለፅ ችግር ምክንያት ሊጭበረበር የነበረ ብር 1 ሚሊዮን 705 ሺህ 473 ብር ከ 30 ሳንቲም እንዲከፈል ተደርጓል ተብሏል ::
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ትኩስ ትኩስ ዜናዎችን፣ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8
በሔኖክ አስራት
ሕዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም











