አሜሪካ ራሺያ ሰራሽ ሚሳዬል መከላከያ ስርአትሽ ውስጥ ተክለሻል ስትል የኔቶ አጋሯ ቱርክ ላይ ማዕቀብ ጥላለች
አሜሪካ እንዳለችው የሩሲያ S-400 ሚሳኤል ከኔቶ ጋር የማይጣጣም ቴክኖሎጂ ሲሆን ከቀዝቃዛው ጦርነት በኋላ የኔቶ አባል ሀገራትና የኔቶ አባል ባለሆኑ ሀገራት መካከል የተመሰረተውን የአውሮፓ አትላንቲክ ወዳጅነት የሚጎዳና ስጋት ላይ የሚጥል መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ማዕቀቡ የቱርክን የመሳርያ ግዢ ማዕቀል ነው ኢላማ ያደረፈው፡፡
እርምጃው በቱርክና በሩሲያ በሚገኙ ባለስልጣናት ተወግዟል፡፡
አሜሪካ F-35 ከተባለው የተዋጋ ጄት ፕሮግራምም ቱርክን አስወጥታታለች፡፡
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8
ድረ ገጻችንን https://ethiofm107.com/ ይጎብኙ::
በጅብሪል ሙሃመድ
ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም











