የአሜሪካ ዲሞክራሲ ሲገፋና አደጋ ላይ እንዲወድቅ ለማድረግ ሲሞከር የነበረ ቢሆንም ፤ እውነተኛ፣ጠንካራና የማይበገር መሆኑን አስመስክሯል ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የህዝቡን ፍቃድና የምርጫውን ውጤት ለመገዳደር እየሞከሩ ነው ያሉ ሲሆን አሁን ጊዜው ገፁን መግለጫ ነው ሲሉ ምክር ለግሰዋቸዋል፡፡
ነጩ ቤተ መንግስት ለመግባት ባይደን ከአሜሪካ የምርጫ ኮሌጅ ማረጋገጫ ማግኘት አለባቸው፡፡
የዲሞክራቱ ጆው ባይደን የህዳርን የምርጫ ፉክክር 306 ድምፅ በማግኘት ነበር 232 ድምፅ ያገኙትን ትራምፕ የረቷቸው፡፡
ውጤቱን መቀበል ያቃታቸው ፕሬዝዳንት ትራምፕ በትዊተር ገፃቸው ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዊሊያም ባርን ማሰናበታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ ምርጫው ተጭበርብሯል ቢሉም ምንም ማስረጃ የለም ብለው ነበር ጠቅላይ አቃቤ ህጉ ::
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8
ድረ ገጻችንን https://ethiofm107.com/ ይጎብኙ:: በሔኖክ አስራት
ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም











