ከአዲስ አበባ ወደ ኤርትራ ተቋርጦ የነበረው የአየር በረራ በዛሬው ዕለት መጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ የተቋረጠው በረራ በዛሬው ዕለት ይጀምራል።

የአየር መንገዱ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ሄኖክ ሲራክ እንደነገሩን በረራው በኮቪድ ምክንያት መቋርጡን አስታውሰዋል ።

አየር መንገዱ ከዛሬ ማለትም ከሰኔ 16 2013 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አስመራ መብረረ ይጀምራል ነው ያሉት።

የኮቪድ 19 መከሰቱን ተከትሎ ወደተለያዩ አገራት ይደረግ የነበረው በረራ መስተጓጎሉ አይዘነጋም ።

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከ20 አመታት ውጥረትና ኩርፊያ በኋላ በመታረቃቸው አየር መንገዱ አገልገሎት መጀመሩ ይታወሳል ።

ይሁን እንጅ ሁለቱ አገራት ከታረቁ በኋላ ድንበሮቻቸውን ከፍተው የነበረ ቢሆንም ወዲያውኑ መዝጋታቸው ይታወቃል ።

ከዚህ ባለፈም የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ክልል እንደሚገኙና የሁለቱ አገራት መሪዎች ወታደሮቹ በቅርቡ ይወጣሉ ብለው ተናግረው የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ስለመውጣታቸው የሚታወቅ ነገር የለም ።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን ቻናላችንን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/ethiofm107dot8 ይቀላቀሉ።
በአባቱ መረቀ
ሰኔ 16 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.