ኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ለሚጠጉ ዜጎች የኮቪድ-19 ክትባት ልትሰጥ ነው፡፡

ኢትዮጵያ እስከ ፈረንጆቹ 2021 መጨረሻ ድረስ ለ22 ሚሊዮን ዜጎች ኮሮና ቫይረስ ክትባት ልትሰጥ መሆኗን አስታውቃለች፡፡

የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳሬክተር አቶ አስቻለው አባይነህ እስከ ፈረንጆቹ 2021 ድረስ 20 ከመቶ የሚሆነው ህዝብ ለመከተብ ታቅዷል ብለዋል፡፡

እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ 2.4 ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎቿን የከተበች ሲሆን በኮቫክስ ጥምረት አማካኝነት 22 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች እስከ 2021 ድረስ ይከተባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ሲሆን በአንድ ሳምንት ብቻ እስከ 10ሺህ ያህል ዜጎች በቫይረሱ እየተያዙ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 308ሺህ 134 የደረሰ ሲሆን 276 ሺህ 842 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

እንደዚሁም 4 ሺህ 675 ያህል ዜጎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ነሐሴ 26 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.