“ሀገር አቀፍ የፆምና የፀሎት ምህላ አዋጅ”

የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አዲሱን አመት በሰላም ለመቀበል ያለመ ለ5 ቀናት የፀሎት መርሐግብር አወጀ።

የፀሎት መርሐ ግብሩ ከጷጉሜ 1 እሰከ 5 የሚቆይ መሆኑም ተገልጿል።

ጉባኤው አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የሰላም ጥሪን በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

አገሪቱ ያጋጠማት ወቅታዊ ችግር በይቅርታና በፍቅር እንዲፈታ የተለያዩ እምነት የሚከተሉ ዜጎች በየሐይማኖታቸው የልዩ ፀሎቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጉባኤው ጥሪ አቅርቧል ሲል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

በሁለቱም ወገኖች ያሉና በትግል ውስጥ ያሉ አካላት ለእርቅ ዝግጁ ሆነው አገሪቷን ማሻገር ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.