ቡሩንዲ ከኢትዮጵያ ግድብ ግንባታ ይልቅ ለግብፃውያን የመኖር መብት ቀዳሚ ነው አለች

ቡሩንዲ የግብፅን የመኖር መብት ከኢትዮጵያ የማልማት መብት ከማግኘት በፊት ሊቀድም ይገባል ብሎ እንደሚያምን የሀገሪቱ ከፍተኛ ዲፕሎማት አስታወቁ።

ኢትዮጵያ ለኢኮኖሚ ዕድገቷ እና ለኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው ብላ በምትከራከረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ነው አስተያየት የሰጡት።

ፕሮጀክቱ በግብፅ እና በሱዳን የውሃ እጥረት እና ደህንነት ላይ ስጋት ፈጥሯል ፣ እነሱም በአባይ ወንዝ ውሃ ላይ ጥገኛ ናቸው ብለዋል አናዶሉ እንደዘገበው።

በመዲናይቱ ካይሮ ከግብፁ አቻቸው ሳሜህ ሹክሪ ጋር በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አልበርት ሺንሺሮ እንደተናገሩት የውሃ ኃይል ፕሮጀክቱ በጣም ስሱ ጉዳይ ቢሆንም የውሃ ተደራሽነት የግብፃውያን “የሕይወት ወይም የሞት” ጉዳይ ነው።

“የመኖር መብት ሁል ጊዜ ከእድገት መብት በፊት መቅደም አለበት ምክንያቱም የሕይወት መብት ከሌለ የልማት መብት ሊከበር አይችልም እዚህ ያለው ምርጫ ግልፅ ነው ”ብለዋል ሺንጊሮ።

ከፍተኛው የቡሩንዲ ዲፕሎማት ጉዳዩን ለመፍታት ወታደራዊ አማራጭን በማስወገድ የግድቡን ውዝግብ በድርድር ፣ በትብብር እና በሕጋዊ ስምምነቶች ለሁሉም ወገኖች በሚስማማ መልኩ መፍታት እንዳለበት አስምሮበታል።

ሺንጊሮ “በዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እና በመልካም ሥራዎች ኃይል እናምናለን” ብለዋል።

በያይኔአበባ ሻምበል
ጳጉሜ 04 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.