ኢትዮጵያና ኬንያ የሞያሌን የአንድ አለቅ የድንበር አገልግሎትን ወደ ሥራ ለማስገባት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

የሁለቱን አገራት የንግድ ትስስር ያጠናክራል የተባለውን የመግባቢያ ስምምነት የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቀበታና፣ የኬንያ የአገር ግዛት ደህንነት ኃላፊና የኬንያ ልዑክ መሪ ዊልሰን ጋቾከኪ በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ የተካሄደው በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ሲሆን ከሁለቱም አገራት የተወጣጡ የግል ዘርፍ ተወካዮች ተገኝተው ውይይት በማድረግ ላይ ናቸው።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት የጉምሩክ ኮሚሾነሩ አቶ ደበሌ ቀበታ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ እና ኬንያ ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረ ግንኙነት እንዳላቸው ገልፀው፣ የሁለቱን አገራት የንግድ ልውውጥ ለማጠናከር የሞያሌ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል።

አገራቱን ድንበር ቢለያያቸውም ንግድ ያስተሳስራቸዋል ያሉት ኮሚሽነሩ፣የሞያሌ የአንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት የንግድ ልውውጡን ከማጠንከሩ ባለፈ ለግሉም ዘርፍ ይበልጥ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።

ስምምነቱ ፣የንግድ፣ የትራንስፖርት፣ እና የዜጎችን እንቅስቃሴ የሚያቀላጥፍ በመሆኑ ለኢትዮጵያና ለኬንያ የንግድ ልውውጥ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነ ዊልሰን ጋቾከኪ ተናግረዋል፡፡

በተለይም የላፕሴት ኮሪደር መገንባት የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንደሚያሳድገውም ነው ኃላፊው ያነሱት።

ባለፈው አመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድና የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሃዋሳ ሞያሌ የጋራ ፍተሻ ጣቢያን መመረቃቸው የሚታወስ ነው።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን ቻናላችንን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/ethiofm107dot8 ይቀላቀሉ።
በአባቱ መረቀ
መስከረም 05 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *