አዲስ አበባ ከተማ አዲስ ምክር ቤት ምስረታ ስነ-ስርአት እየተካሄደ ነው።
በማዘጋጃ ቤት ቴአትር እና ባህል አዳራሽ እየተካሄደ ባለው አዲስ ምክር ቤት ምስረታ ስነ-ስርአት በቀጣይ አምስት ዓመታት ምክር ቤቱን በአፈጉባኤነት እና በምክትል አፈጉባኤ እንዲሁም የከንቲባ ሹመት እና የካቢኔ አባላት ሹመት በቅደም ተከተል ለማካሄድ ባቀደው መሰረት በእጩነት አቅርቧቸው የነበሩት ወ/ሮ ፋይዛ ሞሃመድ 138 ድጋፍ አግኝተው ተሹመዋል፡፡
ወ/ሮ ፈይዛ መሐመድ ዑመር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ነበሩ፡፡
በቀጣይም ምክር ቤቱን በአፈ ጉባኤነት ለአምስት ዓመታት እንዲያገለግሉ ተሹመዋል፡፡
በረድኤት ገበየሁ
መስከረም 18 ቀን 2014 ዓ.ም











