እምብዛም እውቅና የሌለው ራሱን የጅሃዲስት ቡድን በሚል የሚጠራው አዲስ ሃይል ስድስት የሱዳን የስለላ መኮንኖችን መግደሉን በትላንትናው እለት አስታውቋል።
እንደ ቢቢሲ አፍሪካ ዘገባ መንግስት ጥቃቱ ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ ከሚጠራው (አይ ኤስ) ቡድን ታጣቂዎች ጋር እንደሚገናኝ ገልጻል ፡፡
ይህንን የመንግስት ወንጀላ ያጣጣለው ራሱን የስብከት እና የትግል ንቅናቄ ብሎ የሚጠራው ጅሃዲስት ቡድን ከአይ ኤስ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ቢያሳውቅም ጉዳዩን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡
ባለስልጣኖቹ በማክሰኞ ጥቃት አምስት አባሎቻቸው እንደተገደሉባቸው አምነው 11 የቡድኑን ታጣቂዎችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አሳውቀዋል፡፡
ባለፈው ሳምንት የሱዳን ጦር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራን ማክሸፉን ተከትሎ በሽግግር መንግስቱ በሲቪል አስተዳዳሮች እና በወታደራዊ ክንፎች መካከል ያለውን ግንኙነት የበለጠ በይበልጥ መካረሩ እየተነገረ ነው።
ያይኔአበባ ሻምበል
መስከረም 19 ቀን 2014 ዓ.ም











