የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ በወታደራዊ ሃይል የቤት እስረኛ መሆናቸው ተሰማ

ማንነታቸው ያልታወቁ ወታደራዊ ሃይሎች ዛሬ ጠዋት የጠቅላይ ሚኒስትሩን መኖሪያ ቤት በመክበብ ቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸው አልጄዚራ በሰበር ዜናው አስነብቧል ።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪም ሌሎች የካቢኔ አባላት የቤት እስረኛ ስለመሆናቸው ተሰምቷል ።

በአሁኑ ሰዓት የካርቱም መዲናዎች በወታደሮች መዘጋታቸውም ታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ የስልክ ሌሎች መሠረት ልማቶችም አገልግሎት ባለመስጠታቸው በአገሪቱ እየሆነ ያለውን ለማወቅ እንዳልተቻለ አልጄዚራ ዘግቧል ።

ሱዳን ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደምትገኝ የሚታወስ ነው።

ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.