ከየሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ መፈታታቸው ተገለፀ።

በአገሪቱ የተካሄደውን መፈንቅለ መንግሥት የተለያዩ አገራት እና ኅብረቶች ካወገዙት በኋላ የሱዳን ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዱክ ከአንድ ቀን እስር በኋላ ከእስር መፈታታቸው ፍራንስ 24 ዘግቧል

የሱዳን የሽግግር ሉኣላዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፋታህ አልቡርሀን በትላንትናው እለት በሰጡት መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለደኅንነታቸው ሲባል መታሰራቸውን ገልፀው ነገሮች ሲረጋጉ እንደሚፈቱ ተናግረው ነበር።

አልቡርሃን ፥ “ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ እኔ ቤት ነው ያሉት” ያሉ ሲሆን “ይህ የሆነው ለደኅንነታቸው ሲባል ነው” ማለታቸው የሚታወስ ነው።

መፈንቅለ መንግሥት ያደረገው ወታደራዊ ኃይሉ እስከ ሐምሌ 2015 የሲቪሉን አስተዳደር ሥልጣን ቀምቶ ለመቆየት የወሰነ ሲሆን በ10 ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሱዳናዊያን ሥልጣን ለሲቪል አስተዳደር እንዲመለስ በመጠየቅ ተቃውሟቸው ቀጥለዋል

በትላንትናው እለት እንደተለቀቁ የተነገረው ሃምዱክ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ብሊንከን ጋር በስልክ መነጋጋራቸውንም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያውያን
ጥቅምት 17 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.