ወጋገን ባንክ ለልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል አንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡

ባንኩ ድጋፉን ያደረገው የ25ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ይፋዊ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ወቅት ሲሆን ድጋፉ በልብ ህመም ለሚሰቃዩ ህፃናት ህክምና እንዲያገኙ ለማስቻል መሆኑን የባንኩ የዳሬክተሮች የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብድሹ ሁሴን ተናግረዋል፡፡

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ምክንያት በባንኩ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የፈጠረበት ቢሆንም፣ በዚህ አስቸጋሪ ወቅትም ቢሆን ባንኩ ማህበራዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም የቦርድ ሰብሳቢዉ ተናግረዋል፡፡

የልብ ህሙማን ማእከሉ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ህሩይ አሊ ባንኩ ላደረገው ድጋፍ አመስግነዉ ሌሎች ተቋማትና ማህበረሰቡ ለማዕከሉ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

የልብ ማእከሉ አምባሳደር አርቲስት መሰረት መብራቴ የ1 ሚሊየን ብር ቼኩን ከባንኩ የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ አብዲሹ ሁሴን ተረክባለች።

ባንኩ ከዛሬ 25 አመት በፊት በ16 ባለሀብቶችና የተከፈለ 30 ሚሊየን ብር እንዲሁም 60 ሚሊዮን ብር የተፈረመ መነሻ ካፒታል የተመሰረተ ሲሆን በአሁን ወቅት በመላው ሀገሪቱ 398 ቅርጫፎች አሉት፡፡

ወጋገን ባንክ የተከፈለ ካፒታሉ 3.2 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ጠቅላላ ካፒታሉን ደግሞ ወደ 5.5 ቢሊየን ብር አሳድጓል፡፡

በዮርዳኖስ ተሾመ
ጥቅምት 18 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.