“ከትላንት በስቲያ ተዘግቶ የቆየውን የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር አገልግሉት በአስቸኳይ ለመጀመር ርብርብ ላይ ነን “ ኢትዮ- ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር

በርካታ ተሸከርካሪዎች በአዳማ እና በመተሀራ ከተሞች ቆመው እንዳሉና በአከባቢው ከፍተኛ ውጥረት መንገሱን ኤትዮ ኤፍ ኤም ከአከባቢው ነዋሪዎች ሰምቷል፡፡

ነዋሪዎቹ እንደነገሩን በአከባቢው የጸጥታ ችግር መኖሩን ተናግረው ሰዎችም መገደላቸውን ነግረውናል ፣ በዚህ የተነሳ ከድሬዳዋ አዲስ አበባ ከአዲስ አበባ ድሬዳዋ የባቡር አገልግሉት መቋጡን ለጣቢያችን ገልጸዋል፡፡
ኤትዮ ኤፍም ጉዳዩን በተመለከተ ወደ ኢትዮ -ጅቡቲ ባቡር ድርጅት ደውለን ጉዳየጡ የሚመለከታቸውን ሃላፊ ዶ/ር አብዲ ዘነበን አናግሯል፡፡
ዶ/ር አብዲ ‘‘የተፈጠረውን ችግር እያጣራን ነው ፡፡ችግሮን እንዳጣራንም ለደንበኞቻችን እናሳውቃለን” ብለውናል፡፡
ችግሩ ከጽጥታ ጋር የተገናኘ እንደሆነ ለጠየቅናቸው ጥያቄ ዶ/ር አብዲ ‘‘እንዲህ አይነት ችግሮች ካሉ የጸጥታ አካላት ያሳውቃሉ ፣እኛ የሰርቪስ አገልግሎት ነው የምንሰጠው ፣ ከዚህ ጋር የተገናኙ ችግሮች ካሉ ግን እናሳውቃለን” ብለዋል፡፡

‘‘ችግሩ ብዙ የሚያሰጋ አይደለም” ያሉት ዶ/ር አብዲ አገልግሉቱን በአፋጣኝ ለማስጀመር ግን ጥረት ላይ እንደሆኑ ነግረውናል፡፡

መጋቢት 21 ቀን 2014 ዓ.ም
ያይኔአበባ ሻምበል

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *