ታዋቂው የአንበሳ ፋርማሲን በተመለከተ እየሆነ ያለዉ ምንድን ነዉ?

ፋርማሲው ያለበት ህንፃ በቅርስነት የተመዘገበ ነዉ፡፡

ፋርማሲው ያለበት ይህ ታሪካዊ ህንፃ ሊፈርስ ነዉ በሚል ከፍተኛ የተቃዉሞ ድምጾች ሲሰሙ ቆይተዋል፡፡

በዛሬዉ እለት ጠዋት 12፡30 አካባቢ በደረሰን ጥቆማ ማንነታቸዉን ያላወቅናቸዉ ሰዎች ህንጻውን እያፈረሱ ነዉ፤በዉስጡ ያለዉ እቃ እንዲወጣ እንኳን እድል አልሰጡንም ሲሉ ነግረዉናል፡፡

ይህን ያህል አመት ህብረተሰቡን ሲያገለግል የነበረ ፋርማሲ እና በቅርስነት የተመዘገበን የሃገር ሃብት እንዴት ሰዉ ወደ ስራ ሳይሰማራ በሌሊት እንዲፈርስ ይደረጋል? ሲሉም ጥቆማዉን ያደረሱን ሰዎች ይጠይቃሉ፡፡

ስለ ጉዳዩ የተጠየቀዉ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ይህ የሚመለከተዉ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮን ነዉ የሚል ምላሽ ሰጥቶናል፡፡

የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በበኩሉ ጉዳዩ ፖለቲካዊ ይዘት እየያዘ በመምጣቱና ሁሉም በየራሱ ደብዳቤ እየጻፈ በመሆኑ መረጃ እንዳትሰጡ ተብያለሁ ብሎናል፡፡
ነገር ግን የአንበሳ ፋርማሲ የሚታወቀዉ በቅርስነቱ ነዉ፤የማዉቀዉም ይህን ነዉ፤በዛሬዉ እለት ስለተፈጠረዉ ነገርማ ጭራሽ የማዉቀዉ ነገር የለም ሲል ምላሽ ሰጥቶናል፡፡

በዚህ መገፋፋት ዉስጥ ቅርሱን እንዴት መታደግ ይቻላል ስንል ላነሳነዉ ጥያቄ ቢሮዉ ምንም የሚሰጠን መረጃ እንደሌለ ገልጿል፡፡

በሙሉቀን አሰፋ

ሚያዚያ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.