ለተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ የተፈቀደው የ10 ሺህ ብር ዋስትና ተሻረ፡፡
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደላቸውን የ10 ሺህ ብር ዋስትና ተሸሯል።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዋስትና ትዕዛዙ ላይ ይግባኝ ካቀረበ በኋላ ነው።
የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 2፤ 2014 ከሰዓት በጽህፈት ቤት በኩል በሰጠው ትዕዛዝ ለመርማሪ ፖሊስ የ8 ቀናት የምርመራ ጊዜን መፍቀዱን ኢትዮጵያን ኢንሳይደር ዘግቧል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሰኔ 02 ቀን 2014 ዓ.ም











