ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ ከህ/ተ/ም/ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች 6ኛው ምክር ቤት በ1ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በሚያካሂደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቃል የሚሰጡትን ምላሽ ያዳምጣል።

ነገ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ መደበኛ ጉባዔ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተያዘው አጀንዳ መሠረትም፤ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ጥያቄዎችን ያቀርባሉ። እንደዚሁም አስተያየታቸውን ይሰነዝራሉ።

ስብሰባው በቀጥታ ለህዝብ እንደሚተላለፍም ተነግሯል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሰኔ 06 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.