የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ አለማቀፍ አየር ማረፊያ በተፈጠረው ጭጋጋማ አየር ሁኔታ ሳቢያ ከአዲስ አበባ በሚነሱና አዲስ አበባ በሚያርፉ በረራዎች ላይ መዘግየት መፈጠሩን አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ ለተፈጠረው የበረራ መዘግየትና መስተጓጎል ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን፤ ደንበኞቹም አየር መንገዱ ስለኹኔታው የሚያቀርበውን መረጃ እንዲከታተሉ ጠይቋል፡፡
በአባቱ መረቀ
ሐምሌ 04 ቀን 2014 ዓ.ም











