ጠቅላይ ሚኒስትር ራኒል ዊክሪሚስጊ ስሪላንካን በጊዚያዊ ፕሬዝዳንትነት ለመምራት ቃለ ማኃላቸዉን በዛሬዉ እለት ፈፅመዋል፡፡
የአገሪቱ ፕሬዝዳንት የነበሩት ጎታባያ ረጃፓክሳ አመፁን ሽሽት ከአገር መሰደዳቸዉ ይታወሳል፡፡
ጎታባያ በግዞት ላይ እያሉ የመልቀቂያ ደብዳቤ ለአገሪቱ ፓርላማ አስገብተዋል፡፡
ይህንንም ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬዝዳንትነቱን ቦታ ተረክበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ራኒል ዊክሪሚስጊ አገሪቱ የገጠማትን የኢኮኖሚ ዉድቀት ለመፍታት እንደሚሰሩ አስታዉቀዋል፡፡
በአባቱ መረቀ
ሐምሌ 08 ቀን 2014 ዓ.ም











