የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸዉን በቴሌ ብር መክፈል የሚችሉበት ስርዓት ተዘረጋ፡፡

ወደ 300 ሽህ የሚጠጉ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸዉን በቴሌ ብር አማካኝነት መክፈል የሚያስችላቸዉን አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

አሰራሩን ተግባረዊ ያደረጉት ኢትዮ ቴሌኮምና የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በመተባበር ነዉ፡፡

በዚህ የግብር ክፍያ ስርዓት፣የ 2014 በጀት ዓመት ግብራቸዉን የሚከፍሉ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ያለ ምንም እነብግልትና ዉጣ ዉረድ ግብራቸዉን እንዲከፍሉ ያስችላቸዋልም ተብሏል፡፡

አገልግሎቱ ከሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለ ሲሆን እስካሁንም 679 ሰዎች በዚህ ስርዓት ግብራቸዉን ከፍለዋል፡፡

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *