በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ እና ማዕከላዊ ዞኖች በግጭት ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ የውሃ አውታሮች ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቋል፡፡
በግጭት ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የውሃ አውታሮች ወደ ነበሩበት ለመመለስ÷ የውሃ ፓምፖች፣ ጄኔሬተሮች እና የውሃ ማጣሪያ ኬሚካሎችን በመለገስ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መደረጉን የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም











