ዶ/ር ደብረጺዮን ለቪኦኤ እንደተናገሩት ከሰላም ድርድር በፊት መንግሥት ለትግራይ ያቋረጣቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች እንደገና መጀመር እንዳለበት አውስተዋል።
ዶ/ር ደብረጺዮን መንግሥት መሠረታዊ አገልግሎቶችን የሚቀጥልበትን ቁርጥ ያለ ቀን አሜሪካኖች ጠይቀው እንዲነግሯቸው የጊዜ ገደብ መስጠታቸውንም ቪኦኤ ዘግቧል፡፡
መሠረታዊ አገልግሎቶቹ የማይጀመሩ ከሆነ ግን ውጊያ እንከፍታለን ሲሉ ማስጠንቀቃቸዉንም ነዉ ዘገባዉ ያመለከተዉ፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም











