ሕወሃት ከፌደራል መንግሥት ጋር ለሚያደርገው ድርድር ቅድመ ሁኔታና የጊዜ ገደብ ማስቀመጡን የሕወሃት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጺዮን ገ/ሚካዔል ተናገሩ፡፡

ዶ/ር ደብረጺዮን ለቪኦኤ እንደተናገሩት ከሰላም ድርድር በፊት መንግሥት ለትግራይ ያቋረጣቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች እንደገና መጀመር እንዳለበት አውስተዋል።

ዶ/ር ደብረጺዮን መንግሥት መሠረታዊ አገልግሎቶችን የሚቀጥልበትን ቁርጥ ያለ ቀን አሜሪካኖች ጠይቀው እንዲነግሯቸው የጊዜ ገደብ መስጠታቸውንም ቪኦኤ ዘግቧል፡፡

መሠረታዊ አገልግሎቶቹ የማይጀመሩ ከሆነ ግን ውጊያ እንከፍታለን ሲሉ ማስጠንቀቃቸዉንም ነዉ ዘገባዉ ያመለከተዉ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.