ቃላቸውን የጠበቁት የአሜሪካ ኮንግረስ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ በታይዋን ይገኛሉ፡፡
አለም ከአምባገነንነት ዲሞክራሲን መርጧል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም አሜሪካ ያለምንም መወላወል ከታይዋን ጎን መሆኗን አሳይታለች ሲሉም በትዊተር ገፃቸው መልእክት አጋርተዋል፡፡
በመልክእታቸው አሜሪካ ከታይዋን ህዝብ ጎን ናት ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ሁኔታዎች በፍጥነት ተለዋዋጭ በሆነበት የሩቅ ምስራቅ አሜሪካ በግሏ ለቀጠናው ለውጥ እንደምትተጋም አረጋግጣለው ብለዋል፡፡
በአብዱሰላም አንሳር











