የታይዋን ኤርፖርት ከፍተኛ የደህንነት ስጋት ገብቶታል፡፡

ዛሬ በኤርፖርቱ ተቀጣጣይ ነገሮች መገኘታቸውም ተዘግቧል፡፡
ይህም ምናልባት የአሜሪካዋ የኮንግረስ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ይመጣሉ ተብሎ ከመጠበቁ ጋር የተያያዘ ይሆናል እየተባለ ነዉ፡፡

በኤርፖርቱ ሶስት የሚጠጉ ተቀጣጣይ ነገሮች መገኘታቸው የተሰማ ሲሆን አፈጉባኤዋ ወደ ቴፔይ አየር ማረፊያ ማቅናታቸውም እየተሰማ ነው፡፡

የቻይናን ተቃውሞ ተከትሎ በጉዞ ዝርዝራቸው ሳያካትቷት ወደቀጠናው አምርተው ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን እያመሩ ይገኛሉም ተብሏል፡፡
የናንሲን በረራ የሚያሳየው ራዳር 24 የተባለው የአቬሽን በረራዎች የሚያመላክተው ድህረ-ገጽ በመረጃ ጠላፊዎች ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ ሆኗል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሐምሌ 26 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.