የዩክሬን ጦርነት እስከ 2030 ድረስ ሊዘልቅ ይችላል ተባለ፡፡

የዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት እስከ 2030 ሊዘልቅ ይችላል ሲሉ የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ፡፡
የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ቨክቶር ኦርባን ለራዲዮ ዩሮፕ እንደተናገሩት አሁን ባለው ሁኔታ ጦርነቱ በጥቂት ጊዜያቶች የሚጠናቀቅ አይደለም::
ጠቅላይ ሚኒስትር ኦርባን ከፓርቲያቸው ጋር በዝግ ባደረጉት ውይይት፣ ጦርነቱ ለሃንጋሪም እንደተረፈ ተናግረው ጊዜ የሚፈጅ አደገኛ ጦርነት ነው ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ዩክሬን በዚህ ጦርነት ግማሽ ያህል ግዛቷን በሩስያ መወሰዱን ተናግረዉ በዚህ የሚያበቃ አይደለም ሲሉም አክለዋል፡፡

በአውሮፓ ህብረት እና በአሜሪካ ድጋፍ የቀጠለው የዩክሬን ጦርነት፣ አስቸኳይ መፍትሄ የማይገኝለት ከሆነ ከታሰበው በላይ ኪሳራ አሳድሮ የሚያልበት አጋጣሚም ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

አሜሪካ እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀጋራት አሁንም ድረስ ለዩክሬን የጦር መሳርዎችን እየለገሱ ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጦርነቱን ከማፋፋም ውጪ ምንም ለውጥ አላመጣም ብለዋል፡፡
ጦርነቱን ተከትሎ በሩስያ ላይ የተጣሉት ማዕቀቦች ዳፋው ያረፈው እኛን በመሳሰሉ ሃገራት ነው ሲሉ ቪክቶር ኦርባን መናገራቸዉን አርቲ ኒውስ
ዘግቧል፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል

መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.