የሩሲያ የማዕድንና የፖታሽ ማዳበሪያዎች አምራች ዩራልቼም ነዉ ምርቶቹን ለአፍሪካ በነጻ ለማቅረብ መወሰኑን ያስታወቀዉ፡፡
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ዲሚትሪ ኮኒያዬቭ እንዳሉት፣የመጀመሪያው 25 ሺህ ቶን ማዳበሪያ ወደ ቶጎ ይላካል መባሉን አር ቲ ኒዉስ ዘግቧል፡፡

ከዚህ ቀደም የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሃገራቸዉ በምዕራቡ ዓለም በተጣለባት ማዕቀብ ሳቢያ በወደቦች ከተጠራቀመዉ ዉስጥ 300 ሺህ ቶን ማዳበሪያን ለታዳጊ ሀገራት በነፃ ልታቀርብ እንደምትችል ፍንጭ ሰጥተዉ ነበር፡፡
በመሳይ ገ/መድህን
መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም











