ሩሲያ የአፈር ማዳበሪያ ለአፍሪካ በነጻ አቀርባለሁ ብላለች፡፡

የሩሲያ የማዕድንና የፖታሽ ማዳበሪያዎች አምራች ዩራልቼም ነዉ ምርቶቹን ለአፍሪካ በነጻ ለማቅረብ መወሰኑን ያስታወቀዉ፡፡

የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ዲሚትሪ ኮኒያዬቭ እንዳሉት፣የመጀመሪያው 25 ሺህ ቶን ማዳበሪያ ወደ ቶጎ ይላካል መባሉን አር ቲ ኒዉስ ዘግቧል፡፡

ከዚህ ቀደም የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሃገራቸዉ በምዕራቡ ዓለም በተጣለባት ማዕቀብ ሳቢያ በወደቦች ከተጠራቀመዉ ዉስጥ 300 ሺህ ቶን ማዳበሪያን ለታዳጊ ሀገራት በነፃ ልታቀርብ እንደምትችል ፍንጭ ሰጥተዉ ነበር፡፡

በመሳይ ገ/መድህን

መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.