የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ እሁድ ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማክሰኞ መስከረም 17 ቀን ማታ 12:00 ድረስ ምንም አይነት የሞተር እንቅስቃሴ በከተማዋ የተከለከለ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በዚህም ኤጀንሲው የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ አድርጉ ብሏል፡፡
ይሄንን ተላልፈው በሚገኙ ሞተረኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ማለቱን ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም











