በአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የታሪፍ ማሻሻያ ተደረገ፡፡

በነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን ተከትሎ ከጥር 1 ቀን 2015 (ዛሬ) ጀምሮ በአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ መጠነኛ የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ማሻሻያው በጀረጃ 1፣ ደረጃ 2 እና በደረጃ 3 ተሸከርካሪዎች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፤ በአስፋልት እና በጠጠር መንገድ ላይ የሚኖራቸውን እንቅስቃሴ ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡

የአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች በተቀመጠው ታሪፍ ብቻ በማስከፈል አገልግሎት እንዲሰጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

ሕብረተሰቡም ይህን አውቆ ከታሪፍ በላይ የሚጠይቁ አካላትን ለትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች እንዲሁም በየደረጃው ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ሪፖርት በማድረግ ሕግ የማስከበሩ አካል እንዲሆንም የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጠይቋል፡፡

በአባቱ መረቀ
ጥር 01 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.