በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ አልፏል፡፡

ባሳለፍነው ሰኞ በደረሰዉ ርዕደ መሬት በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ 7 መቶ በላይ ማለፉ ተገልጿል፡፡

የቱርክ የአደጋ መከላከል ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ በአገሪቱ የሟቾች ቁጥር ከ 6ሺህ በላይ ሆኗል፡፡

በሶሪያ ያለዉን የሟቾች ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ነገር ግን የአገሪቱ የመንግስት ሚዲያ እንዳስታወቀዉ የሟቾች ቁጥር ከ 2ሺህ 5መቶ በላይ መድረሱን ነዉ ያስታወቀዉ፡፡

በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች ላይ እስካሁን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1 ሺህ 2 መቶ ሀምሳ መድረሱን የሶሪያ የጤና ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡

በአሸባሪዎች ቁጥጥር ስር ባሉ ቦታዎች የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ1ሺህ 2 መቶ 80 በላይ መድረሱን ዘ ዋይት ሄልሜት የተባለ የበጎ ፈቃደኞች ቡድን ገልጿል፡፡

በእስከዳር ግርማ
የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.