ባሳለፍነው ሰኞ በደረሰዉ ርዕደ መሬት በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ 7 መቶ በላይ ማለፉ ተገልጿል፡፡
የቱርክ የአደጋ መከላከል ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ በአገሪቱ የሟቾች ቁጥር ከ 6ሺህ በላይ ሆኗል፡፡
በሶሪያ ያለዉን የሟቾች ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ነገር ግን የአገሪቱ የመንግስት ሚዲያ እንዳስታወቀዉ የሟቾች ቁጥር ከ 2ሺህ 5መቶ በላይ መድረሱን ነዉ ያስታወቀዉ፡፡
በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች ላይ እስካሁን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1 ሺህ 2 መቶ ሀምሳ መድረሱን የሶሪያ የጤና ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡
በአሸባሪዎች ቁጥጥር ስር ባሉ ቦታዎች የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ1ሺህ 2 መቶ 80 በላይ መድረሱን ዘ ዋይት ሄልሜት የተባለ የበጎ ፈቃደኞች ቡድን ገልጿል፡፡
በእስከዳር ግርማ
የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም











