ለ185 ቀናት በጠፈር ላይ የቆየዉ ሩሲያዊው ጠፈርተኛ በኢትዮጵያ ልምዱን እያካፈለ ይገኛል፡፡

ለ185 ቀናት በጠፈር ላይ የቆየዉ ሩሲያዊው ጠፈርተኛ ሰርጌ ሰቨርቺኮቭ በህዋ ሳይንስ ያካበተውን እውቀት እና ልምድ ለኢትዮጵያ ምሁራን እና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አጋርቷል፡፡

የሩሲያን የህዋ ሳይንስ መልካም ልምድ መቅሰም የሚያስችል የልምድ ልውውጥ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡

መርሐ ግብሩ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ፣ በኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና በአዲስ አበባ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን የዘርፉ ምሁራን እና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በልምድ ልውውጡ ተካፍለዋል፡፡

የስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለዘርፉ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኗ አስረድተዋል፡፡

ለተጀመረው ስራም የሩሲያ ልምድ እና አጋዥነት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡

የጠፈርተኛው ልምድ ማጋራትም ኢትዮጵያ ነገ በርካታ የህዋ ሳይንስ ተመራማሪ እንድታፈራ ያነቃቃል ብለዋል።

ዕውቁ የሩሲያዊ ጠፈርተኛ ሰርጌይ ኩድ ስቨርቺኮቭ ከጠፈር ላይ የወሰደውን የዳሎልን ምሥል በአዲስ አበባ ተገኝቶ ለኢትዮጵያውያን ማስረከቡ ይታወሳል።

ሰርጌይ ኩድ ስቨርቺኮቭ ከጠፈር ላይ የወሰደውን የዳሎልን ምሥል በአዲስ አበባ ተገኝቶ ለኢትዮጵያውያን ማስረከቡ ይታወሳል።

በአባቱ መረቀ

መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.