በማደያዎች ላይ ይደረግ የነበረዉ ቁጥጥር ከሶስትዮሽ ርክክብ ከእጅ በነፃ መንገድ በዲጂታል መንገድ ይፈፀማል ተብሏል።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላይ ለጣብያችን እንደገለፁት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመቀናጀት ነደጅ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ ጂፒ ኤስ በመግጠም የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ ነዉ ብለዋል።
የፈሳሽ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ በተገጠመዉ ጂፒ ኤስ የት እንደደረሱ እንዲሁም በሰዓቱ ማደያ መደርሳቸዉንም ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል።
ነዳጅ ማደያዎችንም ቁጥጥር እንደሚደረግ የገለፁ ሲሆን ከሶስተኛ ወገን በነፃ መልኩ ሴንሰር ማደያዎች ላይ በመግጠም ከቢሮ በመሆን የመቋጣጠር ስራ እየሰራ ነዉ ተብሏል።
አሁን እየተተገበረዉ ያለዉ አሰራር ብክነቶችን ከመታደግ አንፃር ፋይዳዉ ከፍ ያለ ነዉ ብለዋል ዋና ዳይሬክተሯ።
ከዛሬ ሚያዝያ 16 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በደጂታል የክፍያ አማራጮች ብቻ ግብይቱ ይፈፀማል መባሉም ይታወሳል።
አቤል ደጀኔ
ሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም











