ሕብረት ባንክ በይቆጥቡ ፣ይቀበሉ፣ይመንዝሩና ይሸለሙ መርሃግብሩ አሸናፊ ደንበኞችን ሸለመ።

ባንኩ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከፍ ለማድረግ ለሶስተኛ ጊዜ ባካሄደው በይቆጥቡ፣በይቀበሉ፣ይመንዝሩና ይሸለሙ መርሃግብሩ የዕጣ አሸናፊ የሆኑትን ደንበኞቹን በዛሬው ዕለት ሸለሟል።

የሕብረት ባንክ ከፍተኛ ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ፅጌሬዳ ተስፋዬ ፣ ባንኩ የደንበኞችን የቁጠባ ባህል እያሳደገ ይገኛል፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ግኝትም ከፍ እንዲል እያደረገ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የባንክ ኢንዱስትሪው የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ደንበኞቹን እያበረታታ ይቀጥላል ነው ያሉት።

በባንኩ የሶስተኛ ዙር ሽልማት አሸናፊ የሆኑ ዕድለኞች ሽልማታቸውን ተረክበዋል።

ሽልማቶቹ ዘመናዊ የቤት አውቶሞቢል ፣ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ፣የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች፣ ፍሪጆች፣ ቴሌቪዥን፣ ወመናዊ ስልኮችና የውሃ መሳቢያ ጄኔሬተር ናቸው።

በአባቱ መረቀ

ግንቦት 25 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.