የአሜሪካ ስሪት የሆነዉ የህንድ ጄት አዉሮፕላን ባጋጠመዉ የሞተር ችግር ነው በሩሲያ የአየር ክልል እንዲያርፍ የተገደደው፡፡
ይህ ክስተት የአሜሪካን ሰንደቅ ዓላማ የያዘች አዉሮፕላን ተመሳሳይ የሞተር ችግር ካጋጠማት አንድ ቀን በኋላ የተፈጠረ በመሆኑ በሩሲያ አየር ክልል አከባቢ ዉጥረት መፈጠሩ ነዉ የተገለጸዉ፡፡
ባሳለፍነው ማክሰኞ የተጠናቀቀዉ አለም ዓቀፉ የኢንዱስትሪ ስብሰባ፣ ወደ ዓለም ዓቀፍ መዳረሻዎች ለሚደረጉ አብዛኞቹ ጉዞዎች በሩሲያ የአየር ክልል ማለፍን እንደ ወሳኝ መሸጋገሪያ አድርጎ ወስዷል፡፡
ይህን ተከትሎ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ዉስጥ ባለችዉ ሩሲያ ላይ ከምዕራባዊያን የተጣለባትን ማዕቀብ ምክንያት በማድረግ፣ ሩሲያ የተወሰኑ አገራትን መለያ የያዙ አዉሮፕላኖች በአየር ክልሏ እንዳያልፉ መወሰኗን ተከትሎ፣ በዚህ የአየር ክልል ማለፍ ግድ የሆነባቸዉ የተለያዩ አገራት በዉሳኔዉ ደስተኛ አለመሆናቸዉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በእስከዳር ግርማ
ሰኔ 01 ቀን ቀን 2015 ዓ.ም











