በጎረቤት ሀገር ሱዳን አዉሮፕላን ተከሰከሰ፡፡

በፖርት ሱዳን አንቶኖቭ አዉሮፕላን ተከስክሶ 9 ሰዎች መሞታቸዉ ተሰምቷል፡፡

በአደጋዉ ህይዎታቸዉን ካጡት መካከል አራቱ ወታደሮች መሆናቸዉ ታዉቋል፡፡
በፖርት ሱዳን ዛሬ ጠዋት ለደረሰዉ የአዉሮፕላን መከስከስ አደጋ መንስኤዉ የቴክኒክ ብልሽት መሆኑን የዘገበዉ አልጄዚራ ነዉ፡፡

አንድ ህፃን ከአደጋዉ መትረፉንም የሀገሪቱ ጦር አስታዉቋል፡፡

በአባቱ መረቀ
ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published.