«ጎዳናዎችን ጽዱ ለማድረግ» ገንዘብ የማሰባሰብ መርኃ ግብር በይፋ ተጀምሯል።

በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ በርካቶች የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉባቸውን የባንክ ማስረጃ እያጋሩ ነው።

አዲስ አበባን ጨምሮ ዋና ዋና የክልል ከተሞችም ይሁኑ ሌሎች የጎዳናም ይሁን የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በተለያየ መጠን የሚገለጽ የንጽህና ችግር እንዳለባቸው ሲነገር ይሰማል።

አዲስ አበባን ጨምሮ ዋና ዋና የክልል ከተሞችም ይሁኑ ሌሎች የጎዳናም ይሁን የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በተለያየ መጠን የሚገለጽ የንጽህና ችግር እንዳለባቸው ሲነገር ይሰማል።

አንዳንድ አካባቢዎች ለጤና ጠንቅ በሚሆን ደረጃ የከፋ መጥፎ ጠረን ወይም ሽታ የሚወጣባቸው አካባቢዎች ጥቂት አይደሉም ። በየመንገዱ ቆሻሻ መጣልም ያን ያህልም ነውር ያልሆነባቸው አካባቢዎች በርካቶች ናቸው።

ከዚህ ሁሉ የከፋው ግን በከተሞች የመጸዳጃ ቤቶች አለመኖር ሰው በየመንገድ ዳር እስከመጸዳዳት የደረሰባቸው እና ከዘመኑ ጋር የማይሄዱ ሰብአዊ ድርጊቶች ሲታይ ችግሩ ምን ያህል አሳሳቢ እንደሆነ በግልጽ ያሳያል ሲል የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት ገልጿል።

ሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *