በኢትዮጵያ ተጨማሪ 150 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ ተጨማሪ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,141 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሃምሳ (150) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሰላሳ ስድስት (1636) ደርሷል፡፡

በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት አራት (4) ሰዎች ከአዲስ አበባ ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን ይህም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ሁለት መቶ ሃምሳ (250) ደርሷል።

እንዲሁም በቫይረሱ ተይዞ የነበረና ተጓዳኝ ህመም የነበረበት የ30 ዓመት ኢትዮጵያዊ ህይወት ያለፈ ሲሆን ይህም ህይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ቁጥር አስራ ስምንት (18) አድርሶታል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/ethiofm107dot8

ግንቦት 27 ቀን 2012 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *