በኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከአራት ሚሊዮን በላይ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት እቅድ ተይዟል።

የፌደራል ፕላን እና ልማት ኮሚሽን የቀጣዮቹ 10 ዓመታት ብሔራዊ እቅድን ከተለያዩ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት እና ምሁራን ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።

በዚህም መሰረት በቀጣዮቹ 10 ዓመታት መንግስት ለዜጎች 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት እቅድ ማስቀመጡ ተገልጿል።

እንደ መንግስት እቅድ ከሆነ እነዚህ ቤቶች የሚገነቡት በአገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ከተሞች ነው ተብሏል።

እነዚህ መኖሪያ ቤቶች የሚገነቡትም በመንግስት እና በግል ባለሃብቱ ትብብር እንደሚሆንም ተገልጿል።

በዚህ እቅድ መሰረት ከአስር ዓመት በኋላ ለሁሉም ዜጎች ንጹሁ መጠጥ ውሃ ለማቅረብም መታቀዱን ከኮሚሽኑ ሰምተናል።

በዳንኤል መላኩ
ሐምሌ 8 ቀን 2012 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *