በኢትዮጵያ ጎረቤት አገራት የፖሊዮ ቫይረስ መከሰቱን ተከትሎ ለአራት ቀናት የሚቆይ አገር አቀፍ ክትባት ሊሰጥ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

በ4 ክልሎች እና በ2ቱ ከተማ መስተዳደሮች ከመስከረም 27 እስከ መስከረም 30 ቀን 2013 ዓ.ም የፖሊዮ ክትባት እንደሚስጥ ፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

የፖሊዮ ቫይረሱ ከኢትዮጵያ ጠፍቶ የነበረ ቢሆንም ከጎረቤት ሀገራት በመጣ ቫይረስ ማገርሸቱ ተነግሯል ።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አስቻለው አባይነህ እንዳሉት ሁለቱን ከተማ መስተዳደሮች ጨምሮ በሱማሌ ፣ በኦሮሚያ ፣በደቡብ እና በሀረር ክልል የፖሊዮ ክትባቱ ይሰጣል ብለዋል ።

ክትባቱ ቤት ለቤት የሚካሄድ ሲሆን ከ5 አመት በታች የሆኑ 7 ሚሊየን ሕጻናት ይከተባሉ ተብሏል ።

ከዚህ በፊት የተከተቡ ህጻናትም ቢሆኑ በዘመቻው ይከተባሉ ተብሏል ።

የቢጫ ወባ ክትባትም በደቡብ እና በኦሮሚያ ክልሎች ከጥቅምት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ አቶ አስቻለው ተናግረዋል ።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በዳንኤል መላኩ
መስከረም 22 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *