ምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአቶ ልደቱ አያሌው ክስ መዝገብ ምስክሮችን ፖሊስ በቀጠሮ ቀን ይዞ እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጠ።

ዛሬ አቃቤ ህግ አሉኝ ያላቸውን ምስክሮች ቃል ለመስማት በምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው ውሳኔ ሳያገኙ ተመልሰዋል፡፡

የአቶ ልደቱ ጠበቃ የሆኑት አቶ አብዱል ጀባር ሁሴን ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ፍርድ ቤቱ ለምን አቃቤ ህግ ምስክሮቹን እንዳላቀረበ ሲጠይቅ ሁለቴ ቀርበው ስለተመለሱብኝ ዛሬ አልመጡም ሲል መልሷል ብለውናል ፡፡

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በመያዝ ክስ የተመሰረተባቸው አቶ ልደቱ የዋስትና መብታቸው ሳይከበር ቀርቷል፤ ይህም በእጅጉ አሳዛኝ ነው ብለዋል ጠበቃው ፡፡

እናም ፖሊስ እና አቃቤ ህግ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ያከብሩ ዘንድ ፍርድ ቤቱ በአጽንኦት እና ከማስጠንቀቂያ ጋር ትዕዛዝ እንዲሰጥ ጠይቀናል ነው ያሉት አቶ አብዱል ጀባር ፡፡

ፍርድ ቤቱ ምስክሮቹ መጥሪያ እንዲሰጣቸው እና እንዲቀርቡ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለቢሾፍቱ ወረዳ ፖሊስ መምሪያ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ማዘዙን አስረድተዋል፡፡

የምስክሮቹን ቃል ለመስማትም ለጥቅምት 5 ቀን 2013 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል ፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በያይኔአበባ ሻምበል
ጥቅምት 3 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *