ከቻይና ጋር ከፍተኛ ዉዝግብ ዉስጥ የገባችዉ አሜሪካ ለታይዋን 3 ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ለመሸጥ ማረጋገጫ ሰጠች፡፡

ቀደም ሲል አሜሪካ ለታይዋን የመሬትና የአየር ላይ ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎችን ጨምሮ፣ 7 ዘመናዊ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን እንደምትሸጥ ገልጻ የነበረ ሲሆን፣ ከዚያ ዉስጥ 3ቱን ለታይዋን ለመሸጥ ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች፡፡

አሁን ለሽያጭ ዝግጁ የሆኑት አንድ ክሩዝ ሚሳኤል፣ኤፍ 16 የጦር ጀትና እስከ 190 ማይል ድረስ ጠላትን ማጥቃት የሚችል ሮኬት ናቸዉ፡፡

በአሜሪካ የቻይና ኤምባሲ የትራምፕ አስተዳደር የያዘዉን ለታይዋን መሳሪያ የመሸጥ እቅድ እንዲሰርዝ ጠይቋል፡፡

ቻይና በሉዓላዊነቴ ላይ የተቃጣ ጣልቃ ገብነት ነዉ በሚል ይህን የአሜሪካን ድርጊት ስትኮንን ብትቆይም ከአሜሪካ በኩል ግን ሰሚ አላገኘችም፡፡

ታይዋን አሁን ለሽያጭ ዝግጁ ናቸዉ ለተባሉ የጦር መሳሪያዎች ምን ያህል እንደምትከፍል ባይገለጽም ቀደም ሲል ተዋጊ ጀቶችን ለመግዛት ከአሜሪካ ጋር የ 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ማድረጓ ይታወሳል፡፡

የአሜሪካ ዉሳኔ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ዉጥረት ዉስጥ እንዳይከተም ስጋት መፍጠሩን ሮይተርስ ዘግቧል።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በዳንኤል መላኩ
ጥቅምት 3 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *